ነገሌ, መጋቢት 3 ቀን 2002 (ነገሌ) - የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት / መኢአድ/ በጉጂ ዞን በመጪው ግንቦት ወር በሚካሄደው ብሄራዊ ምርጫ ለመወዳደር በዞን ደረጃ ጽህፈት ቤት ከፍቶ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን አስታወቀ፡፡
በድርጅቱ የጉጂ ዞን ጽህፈት ቤት ዋና ጸሐፊ መቶ አለቃ ንጉሴ ሰለሞን ለኢዜአ.እንደገለጹት ድርጅቱ በዞኑ ነገሌ ቦረና ከተማ ካለፈው ታህሳስ ወር ጀምሮ ጽህፈት ቤት ከፍቶ በምርጫው ለመወዳደር እየሰራ ነው፡፡
በዞኑ በኡራጋ፣ በቦሬ፣ ቀርጫ ወረዳዎችና በነገሌ ቦረና ከተማ ድርጅቱን ወክለው የሚወዳደሩ ለህዝብ ተወካዬች ምክር ቤት አምስት
ለክልል ምክር ቤት ደግሞ አስር እጩዎች ማስመዝገቡን አስታውቀዋል፡፡
እንደ መቶ አለቃ ንጉሴ ማብራሪያ የዕጩዎቹ ስም ዝርዝር በግልጽ በሚታይበት ቦታ ተለጥፎ ለህዝብ ይፋ ሆኗል፡፡
በተጨማሪም ድርጅቱ በሂደት የሚያጋጥሙ ችግሮችን በውይይት በመፍታት ምርጫው ሰላማዊ፣ ፍትሃዊ፣ዴሞክራሲያዊና በሁሉም
ዘንድ ተዓማኒ እንዲሆን ከኦህዴድ/ኢህአዴግ ጋር የጋራ ምክር ቤት አቋቁሞ አብሮ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ሪፖ ኤዲ፣ከ9፡00-9፡40፣አጥ
---END---