ጎንደር, መጋቢት 3 ቀን 2002 (ጎንደር) - በጎንደር ከተማ በመጪው ግንቦት ወር ለሚካሄደው ምርጫ የሚወዳደሩ ዕጩዎች ስም ዝርዝር ለህዝብ ይፋ ሆነ። የዞኑ ምርጫ ቦርድ ጽህፈት ቤት አስተባባሪ አቶ ቢትወደድ ተስፋዬ ትናንት ለኢዜአ.እንደገለጹት በከተማው ስድስት የፖለቲካ ፓርቲዎች ለተወካዮችና ለክልል ምክር ቤት 31 ዕጩዎችን አቅርበዋል።
በከተማው እጩዎቻቸውን ያስመዘገቡት የሚወዳደሩት ብአዴንን ጨምሮ መኢአድ፣ኢዴፓ፣ ኢራፓ ፣መድረክና ቅንጅት መሆናቸውን ጠቁመዋል ።
የፖለቲካ ፓርቲዎቹ ያቀረቧቸው የእነዚሁ ዕጩዎች በየምርጫ ጣቢያው ስም ዝርዝራቸው ለህዝብ ይፋ እንዲሆን መደረጉን
ገልጸዋል።
ሪፖ/ኤዲ/ 8.20-8.30 ጠሰድ=0.10 ጥ/መካ/
---END---