አዲስ አበባ, የካቲት 1 ቀን 2002 (አዲስ አበባ) - ፓርቲዎች የምርጫ ቅሰቀሳ የሚያደርጉበት ነፃ የአየር ሰዓት ድልድልና የጋዜጣ ዓምድን የተመለከተ ዕጣ በዛሬው ዕለት ለማውጣት ተይዞ የነበረው ፕሮግራም በፓርቲዎች ጥያቄ መሠረት ለሌላ ጊዜ ተላለፈ፡፡ፕሮግራሙ ሊተላለፍ የቻለው ፓርቲዎች ከአባሎቻችንና ከአመራሩ ጋር በተዘጋጀው የፖለቲካ ፓርቲዎች የመገናኛ ብዙሃን መመሪያ ላይ እንወያይ የሚል ጥያቄ በማንሳታቸው ነው፡፡
በዚህ መሠረት ፓርቲዎቹ ፕሮግራሙን በመጪው ረቡዕ ለማካሄድ ቀጠሮ ይዘዋል፡፡
ፕሮግራሙ የተዘጋጀው በኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለሥልጣንና በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነው፡፡
ሪ1.00ያ1.05
---END---